የብዙዎችን ሕይወት የሚታደገው አጋር ኢትዮጵያ ከአማራ ክልል ጋር አዲስ የሴፍ ሀውስ ርክክብ ስምምነት ተፈራረመ።

ባህር ዳር – ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከስደት ተመላሽ የሆኑ፣ በሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር የተጎዱ እንዲሁም ልዩ ልዩ ጥቃቶች የደረሰባቸው ከ240 ሺህ በላይ ዜጎችን ከቀውስ የታደገው አንጋፋው ሀገር በቀል ድርጅት አጋር ኢትዮጵያ፤ በአማራ ክልል የሚሰጠውን ሁለንተናዊ የሰብአዊ ድጋፍ አገልግሎት ይበልጥ ለማስፋፋት የሚያስችለውን ታሪካዊ የስምምነትና የህንፃ ርክክብ በባህር ዳር ከተማ በይፋ ፈጽሟል። ተቋሙ በተለይ ለአደጋ ተጋላጭ ወገኖች […]